Timran

በትምራን አዘጋጅነት በመሰጠት ላይ የሚገኘው የፖለቲካ ተግባቦት የምርጫ ቅስቀሳ ዘመቻ ክሂሎት ሥልጠና ቀጥሏል

በትምራን አዘጋጅነት ለኢትዮጵያ ሴት ፖለቲካ ፓርቲ አባላት ጥምረት ከየካቲት 28 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በመሰጠት ላይ የሚገኘው የፖለቲካ ተግባቦት እና የምርጫ ቅስቀሳ ዘመቻ ክሂሎት ሥልጠና ቀጥሏል።

በሁለተኛ እና ሦስተኛ ቀን ውሎ ፖለቲካዊ የምርጫ ቅስቀሳ ዘመቻ ተግባቦት ጋር በተያያዘ መራጮችን የማሳመን ፖለቲካ ቅስቀሳ ዘመቻ፣ ዕጩ መራጮችን የማሳመን ሂደቶች እና ብልሃቶች እንዲሁም የፖለቲካ ትረካዊ የምርጫ ቅስቀሳ የማሳመን ስልት እና የፖለቲካዊ ተግባቦት የማሳመን አተገባበር በሚሉ ርእሰ ጉዳዮች ሥልጠናው እየተሰጠ ይገኛል።

ከሲቪክ ማኅበራት ድጋፍ ፕሮግራም 2 በተገኘ የገንዘብ እገዛ እየተሰጠ ያለው ሥልጠና በነገው ዕለት ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።

Share this post on

Share on facebook
Share on telegram
Share on whatsapp
Share on pinterest
Share on twitter
Share on linkedin
Share on skype
Share on print

Latest Posts