Timran

ትምራን ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ሴት ባለሞያዎች እና ሴታዊት ጋር የመልእክት ማጥራት ምክክር አካሄደች

ትምራን ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ሴት ባለሞያዎች እና ሴታዊት ጋር በመሆን ሴቶች በሀገራዊ ምክክር መድረክ ላይ ስለሚኖራቸው ሚና በተመለከተ የመልእክት ማጥራት ምክክር መጋቢት 04 ቀን 2015 ዓ.ም በሐርመኒ ሆቴል አካሄደች።

የመልእክት ማጥራት ምክክሩ የካቲት 15 ቀን 2015 ዓ.ም የተካሄደውን ውይይት ተከትሎ የመጣ ነው።

በምክክሩ ላይ ተለይተው የተጣሩት መልእክቶች ሴቶች በብሔራዊ ምክክሩ ላይ  ሊኖራቸው ስለሚገባው ሚና እንደ ሚዲያው ዓይነት ተቀርፀው ይሰራጫሉ።

ትምራን፣ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ሴት ባለሞያዎች እና ሴታዊት በሀገራዊ ምክክር መድረክ ሂደት ውስጥ ሴቶች ትርጉም ያለው ተሳትፎ እንዲኖራቸው ለማስቻል በ50 የሲቪክ ማኅበራት የተመሠረተው ጥምረት ለሴቶች በሀገራዊ ምክር መድረክ አባል ናቸው።

Share this post on

Share on facebook
Share on telegram
Share on whatsapp
Share on pinterest
Share on twitter
Share on linkedin
Share on skype
Share on print

Latest Posts